ካንሳስ ሲቲ ኢትዮዽያዊያን ሰባተኛ ቀን  አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን ሰላምታችን ይድረሳችሁ!!

በየሳምንቱ የሰንበት ዕለት፥የሰንበት ትምህርት  አገልግሎት በ 9:30 AM
የስብከት አገልግሎት በ 11:00 AM
እንዲሁም ደግሞ አርብ ማታ በ 7:30 PM እና ቅዳሜ ከሰዓት በ 5:00 PM አገልግሎት የሚኖረን ሲሆን፥

በአሁኑ ጊዜ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ይህ አገልግሎት በቴሌ ኮንፍራንስ
ስልክ ቁጥር ፥ 605472 5414 ኮድ 767832 እና በዩቱብ የሚተላለፍ መሆኑን ልንገልፅላችሁ እንወዳለን።

 

“ለአህዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግስት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል
በዚያን ጊዜ መጨረሻው ይመጣል።”
የማቴዎስ ወንጌል 24:14

ከላይ ባለዉ መዉጫ(MENU)  የሚገኙትን አርዕስቶች በመጫን 
ለናንተ ያለንን በበለጠ እወቁ።

የዓለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን ቤተ-ሰብ 

የሰባተኛው ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን በሰሜን አሜሪካ ከአንድ ሚሊዮን በላይ አባላትን ጨምሮ በመላው ዓለም ከ 19 ሚሊዮን በላይ አባላት ያሉት ዋና የፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያን ናት። የአድቬንቲስት ቤተክርስትያን በአጠቃላይ 173 ሆስፒታሎች እና ሕንፃዎች እንዲሁም በዓለም ዙሪያ ከ 7,500 በላይ ትምህርት ቤቶች ይሠራል ።  አድቬንቲስት ልማት እና መልሶ ማቋቋም ኤጀንሲ (ማኅበራዊ ልማት) እና የኣደጋ ጊዜ እጦትን ለመንካት ከ 130 በላይ በሆኑ ሀገራት ማህበረሰብ ውስጥ ይሰራል።

 

Kansas City Ethiopian SDA Church
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.